ባንካችን በጅማ ከተማ ማዕድ የማጋራት መርሃ ግብር አካሄደ

Share the Post:

ግሎባል ባንክ ኢትዮጵያ 1447ኛውን የረመዳን ፆም ምክንያት በማድረግ በጅማ ከተማ ድጋፍ ለሚሹ የማህበረሰብ አካላት ማዕድ የማጋራት መርሃ ግብር መጋቢት 6 ቀን 2018 ዓ.ም በቡካሪ መስጂድ  አከናውኗል።

ግሎባል ባንክ ኢትዮጵያ ማህበራዊ ኃላፊነቱን መወጣት የባንኩ ዋነኛ እሴት አድርጎ እየሰራ እንደሚገኝ የገለፁት የባንካችን ኮርፖሬት ባንኪንግ ቺፍ ኦፊሰር አቶ ሳኅለሚካኤል መኮንን ዛሬ ያካሄድነው ማዕድ የማጋራት መርሃ ግብር ይኸንኑ ዕሴት የሚያጠናክር ነው ብለዋል።

ዛሬ የተደረገው ድጋፍ የረመዳን ወር የሚያስተምረውን የመረዳዳት እና የመተጋገዝ እሴት መሠረት በማድረግ መሆኑን በመርሃ ግብሩ ወቅት የገለፁት አቶ ሳኅለሚካል፤ ዝቅተኛ ገቢ ያላቸው ወገኖች የጾም ወራቸውን ያለስጋት እንዲያሳልፉ ያስችላል ብለዋል።

የጅማ ከተማ እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት ኃላፊ ሼህ መሐመድ አሚን በበኩላቸው ባንኩ በረመዳን ወር ላሳየው አጋርነት ምስጋናቸውን አቅርበው የሚደረገው ድጋፍ በቀጣይም ተጠናክሮ እንዲቀጥል ጠይቀዋል።

ግሎባል ባንክ ኢትዮጵያ ማህበራዊ ኃላፊነቱን የመወጣት ተግባሩን አጠናክሮ እንደሚቀጥልና ከህዝቡ ጎን መሆኑን በተግባር እንደሚያረጋግጥ ያመላከቱት ደግሞ የማርኬቲንግ እና ኮምዩኒኬሽንስ ዳይሬክተር አቶ ቢኒያም ፍቃዱ ናቸው።

ዛሬ በተከናወነው ማዕድ ማጋራት ዝቅተኛ ገቢ ላላቸው 80 ሰዎች የተለያየ ድጋፍ ተደርጎላቸዋል።

በማዕድ ማጋራት መርሃ ግብሩ የባንካችን ቺፍ ኮርፖሬት ባንኪንግ ኦፊሰር አቶ ሳኅለሚካኤል መኮንን፣ የባንካችን ከፍተኛ የሼሪዓ አማካሪ ሼህ ሚስባህ አብዱራህማን ፣ የጅማ ከተማ እስልምና ጉዳዮች ም/ቤት ኃላፊ ሼህ መሐመድ አሚን፣ የማርኬቲንግ እና ኮምዩኒኬሽንስ ዳይሬክተር አቶ ቢኒያም ፍቃዱ፣ ከወለድ ነፃ የባንክ አገልግሎት ዳይሬክተር ሱሌማን አብደላ እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።

ግሎባል ባንክ ኢትዮጵያ
ለጋራ ስኬታችን!

Related Posts

ግሎባል ባንክ ኢትዮጵያ በድሬዳዋ ከተማ ለደንበኞቹ የኢፍጣር ፕሮግራም አዘጋጀ

ግሎባል ባንክ ኢትዮጵያ የመተሳሰብ ተምሳሌት የሆነውን የረመዳን ፆም ምክንያት በማድረግ በድሬዳዋ ከተማ ለሚገኙ ደንበኞች የኢፍጣር መርሃ-ግብር...

ግሎባል ባንክ ኢትዮጵያ በጅማ ከተማ ለሚገኙ ከወለድ ነፃ የባንክ አገልግሎት ደንበኞች የኢፍጣር መርሃ ግብር አካሄደ

1447ኛውን የረመዳን ፆም ምክንያት በማድረግ መጋቢት 6 ቀን 2018 ዓ.ም  በለይሌ ሪዞርት በተሰናደው የኢፍጣር መርሃ ግብር የባንካችን...

ግሎባል ባንክ ኢትዮጵያ ከጅማ ከተማ እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት ጋር በጋራ መስራት በሚቻልበት ምቹ ሁኔታዎች ዙሪያ ውይይት አደረገ።

ግሎባል ባንክ ኢትዮጵያ እና የጅማ ከተማ እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት በተለያዩ ዘርፎች በጋራ መስራት በሚቻልበት ምቹ ሁኔታዎች ዙሪያ የሁለቱም...