
1447ኛውን የረመዳን ፆም ምክንያት በማድረግ መጋቢት 6 ቀን 2018 ዓ.ም በለይሌ ሪዞርት በተሰናደው የኢፍጣር መርሃ ግብር የባንካችን ኃላፊዎች፣ ደንበኞች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።
ግሎባል ባንክ ኢትዮጵያ የደንበኞችን ፍላጎት ማዕከል ያደረግ ምቹ እና ቀልጣፋ የባንክ አገልግሎት እየሰጠ መሆኑን በመርሃ ግብሩ ወቅት የገለፁት ቺፍ ኮርፖሬት ባንኪንግ ኦፊሰር አቶ ሳኅለሚካኤል መኮንን በቀጣይም የደንበኞቻችንን ፍላጎት የሚያሟላ አገልግሎት ለመስጠት ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መሆንን አመላክተዋል።
በኢፍጣር መርሃ ግብሩ ተሳታፊ የሆኑ የባንካችን ከወለድ ነፃ ደንበኞች በበኩላቸው ባንኩ ለአዘጋጀው ኢፍጣር ምስጋናቸውን አቅርበው በቀጣይም ከባንኩ ጋር ያላቸውን የስራ ትስስር ይበልጥ እንደሚያጠናክሩ ተናግረዋል።
1447ኛውን የረመዳን ፆም ምክንያት በማድረግ ባንካችን በተለያዩ ከተሞች ማዕድ የማጋራት እና የኢፍጣር መርሃ ግብር እያከናወነ ይገኛል።
ግሎባል ባንክ ኢትዮጵያ
ለጋራ ስኬታችን!