Search
Close this search box.

ግሎባል ባንክ ከግሮቭ ጋርደን ጋር በመተባበር ሴት ነጋዴዎች ብቻ ተሳታፊ የሚሆኑበትና ለሁለት ወራት የሚቆይ የንግድ ባዛርን ስፖንሰር አደረገ::

Share the Post:
ግሎባል ባንክ ይህን ከጁምዓ እስከ ሰንበት በሚል ስያሜ የተዘጋጀውን እና ለመጀመሪያ ጊዜ የተሰናዳውን የነጋዴ ሴቶች የንግድ ባዛር በብቸኛ አጋርነት አዘጋጅቷል፡፡
ግሎባል ባንክ ባዛሩን ድጋፍ ያደረገባቸው ዋና ዋና ዓላማዎች፡-
  • በንግድ ላይ የተሰማሩ ሴቶች ስራቸው ጎልቶ የሚወጣበትን አጋጣሚ መፍጠር
  • በኮቪድ-19ና በሌሎችም ምክንያቶች ተቀዛቅዞ የነበረው የቢዝነስ እንቅስቃሴ ላይ መነቃቃት ለመፍጠር
  • ከተለያዩ የንግዱ ማህበረሰብ አካላት ጋር ተቀራርቦ መስራት ለስኬት መሰረት በመሆኑ
  • በአገር ደረጃ እየተካሔዱ ባሉ የህብረተሰቡን ሕይወት ሊለውጡ በሚችሉ ማህበራዊ እንቅስቃሴዎች በመሳተፍ የበኩሉን አስተዋጽዖ ማበርከት የባንካችን የዘወትር ተግባሩ በመሆኑ
  • እንደ መልዕክታችን ለሴቶች የእድገት መሰላል መሆናችንን ለማሳየት
  • ሴቶችን ማገዝ የአጠቃላይ ማህበረሰቡን፣ ብሎም የአገርን እደገት ማገዝ ነው ብለን ስለምናምን
ባንካችን ለማህበራዊ ጥሪዎች ፈጣን ምላሽ መስጠቱን፣ ከማህበረሰቡ ጋር አብሮ ማደጉን አጠናክሮ ይቀጥላል፡፡