ግሎባል ባንክ ይህን ከጁምዓ እስከ ሰንበት በሚል ስያሜ የተዘጋጀውን እና ለመጀመሪያ ጊዜ የተሰናዳውን የነጋዴ ሴቶች የንግድ ባዛር በብቸኛ አጋርነት አዘጋጅቷል፡፡
ግሎባል ባንክ ባዛሩን ድጋፍ ያደረገባቸው ዋና ዋና ዓላማዎች፡-
- በንግድ ላይ የተሰማሩ ሴቶች ስራቸው ጎልቶ የሚወጣበትን አጋጣሚ መፍጠር
- በኮቪድ-19ና በሌሎችም ምክንያቶች ተቀዛቅዞ የነበረው የቢዝነስ እንቅስቃሴ ላይ መነቃቃት ለመፍጠር
- ከተለያዩ የንግዱ ማህበረሰብ አካላት ጋር ተቀራርቦ መስራት ለስኬት መሰረት በመሆኑ
- በአገር ደረጃ እየተካሔዱ ባሉ የህብረተሰቡን ሕይወት ሊለውጡ በሚችሉ ማህበራዊ እንቅስቃሴዎች በመሳተፍ የበኩሉን አስተዋጽዖ ማበርከት የባንካችን የዘወትር ተግባሩ በመሆኑ
- እንደ መልዕክታችን ለሴቶች የእድገት መሰላል መሆናችንን ለማሳየት
- ሴቶችን ማገዝ የአጠቃላይ ማህበረሰቡን፣ ብሎም የአገርን እደገት ማገዝ ነው ብለን ስለምናምን
ባንካችን ለማህበራዊ ጥሪዎች ፈጣን ምላሽ መስጠቱን፣ ከማህበረሰቡ ጋር አብሮ ማደጉን አጠናክሮ ይቀጥላል፡፡
![](https://debubglobalbank.com/wp-content/uploads/2021/03/157375119_257794715883492_3316983260982990874_o-4-300x225.jpg)
![](https://debubglobalbank.com/wp-content/uploads/2021/03/157222489_257794709216826_2797585458763856095_o-300x200.jpg)
![](https://debubglobalbank.com/wp-content/uploads/2021/03/156702188_257794725883491_9055545814762442110_o-300x225.jpg)