ግሎባል ባንክ ከግሮቭ ጋርደን ጋር በመተባበር ሴት ነጋዴዎች ብቻ ተሳታፊ የሚሆኑበትና ለሁለት ወራት የሚቆይ የንግድ ባዛርን ስፖንሰር አደረገ::

Share the Post:
ግሎባል ባንክ ይህን ከጁምዓ እስከ ሰንበት በሚል ስያሜ የተዘጋጀውን እና ለመጀመሪያ ጊዜ የተሰናዳውን የነጋዴ ሴቶች የንግድ ባዛር በብቸኛ አጋርነት አዘጋጅቷል፡፡
ግሎባል ባንክ ባዛሩን ድጋፍ ያደረገባቸው ዋና ዋና ዓላማዎች፡-
  • በንግድ ላይ የተሰማሩ ሴቶች ስራቸው ጎልቶ የሚወጣበትን አጋጣሚ መፍጠር
  • በኮቪድ-19ና በሌሎችም ምክንያቶች ተቀዛቅዞ የነበረው የቢዝነስ እንቅስቃሴ ላይ መነቃቃት ለመፍጠር
  • ከተለያዩ የንግዱ ማህበረሰብ አካላት ጋር ተቀራርቦ መስራት ለስኬት መሰረት በመሆኑ
  • በአገር ደረጃ እየተካሔዱ ባሉ የህብረተሰቡን ሕይወት ሊለውጡ በሚችሉ ማህበራዊ እንቅስቃሴዎች በመሳተፍ የበኩሉን አስተዋጽዖ ማበርከት የባንካችን የዘወትር ተግባሩ በመሆኑ
  • እንደ መልዕክታችን ለሴቶች የእድገት መሰላል መሆናችንን ለማሳየት
  • ሴቶችን ማገዝ የአጠቃላይ ማህበረሰቡን፣ ብሎም የአገርን እደገት ማገዝ ነው ብለን ስለምናምን
ባንካችን ለማህበራዊ ጥሪዎች ፈጣን ምላሽ መስጠቱን፣ ከማህበረሰቡ ጋር አብሮ ማደጉን አጠናክሮ ይቀጥላል፡፡

Related Posts

ግሎባል ባንክ ኢትዮጵያ ከደንበኞች ጋር ያለውን ስትራቴጂካዊ አጋርነት ማጠናከር ዋነኛ መርህ አድርጎ እየሰራ ነው – ዶ/ር ተስፋዬ ቦሩ

ግሎባል ባንክ ኢትዮጵያ ከደንበኞች ጋር ያለውን ስትራቴጂካዊ አጋርነት በማጠናከር ለጋራ ስኬት በጋራ መስራት ዋና ዕሴት አድርጎ እየሰራ መሆኑን...

ባለፉት ዘጠኝ ወራት አመርቂ ዉጤት መመዝገቡ ተገለፀ

ግሎባል ባንክ ኢትዮጵያ ባለፉት 9 ወራት በበርካታ መለኪያዎች አመርቂ ውጤት ማስመዝገቡን የባንኩ የቦርድ አመራር እና የማኔጅመንት አባላት ገለጹ፡፡...

ግሎባል ባንክ ኢትዮጵያ የተሳተፈበት ዓለም አቀፍ የኦቲዝም ቀን በደማቅ ሁኔታ ተከበረ

ነህሚያ የኦቲዝም ማዕከል የ2018 ዓ.ም የኦቲዝም ግንዛቤ ማስጨበጫ መርሃ-ግብርን ሚያዚያ 18 ቀን 2018 ዓ.ም በተለያዩ ዝግጅቶች አከናውኗል።...