የሁለት ሚሊዬን ብር ድጋፍ ተደረገ !!!

Share the Post:

የሁለት ሚሊዬን ብር ድጋፍ ተደረገ !!!

ግሎባል ባንክ ኢትዮጵያ ለመቄዶንያ የአረጋውያንና አዕምሮ ህሙማን መርጃ ማዕከል ብር ሁለት ሚሊዬን በማዕከሉ ዋና መስሪያ ቤት በመገኘት ጥቅምት 22 ቀን 2017 ዓ.ም ድጋፍ እና ጉብኝት አድርጓል፡፡

“ለህብረተሰቡ መስጠት” የግሎባል ባንክ ኢትዮጵያ አንዱ ዕሴት መሆኑን ድጋፉን ባበረከቱበት ወቅት ያወሱት የግሎባል ባንክ ኢትዮጵያ ቺፍ ኮርፖሬት ባንኪንግ ኦፊሰር አቶ ሳህለሚካኤል መኮንን የዛሬው ድጋፍም ባንካችን ለወገኖቹ ብርቱ አጋር መሆኑን ያሳየበት የድጋፍ መርሃ ግብር ነው ብለዋል ፡፡

ግሎባል ባንክ ኢትዮጵያ ድጋፍ ሲያደርግ ለመጀመሪያ ጊዜ አይደለም የመጨረሻውም አይሆንም ያሉት አቶ ሳኅለሚካኤል በቀጣይም ድጋፍ ለሚያስፈልጋቸው ተቋማት እና የማህበረሰብ ክፍሎች ድጋፍ ማድረጉን እንደሚቀጥል ተናግረዋል ፡፡

የመቄዶንያ የአረጋውያን እና አዕምሮ ሕሙማን መርጃ ማዕከል መስራች ክቡር ዶክተር ብንያም በለጠ በበኩላቸው ባንኩ ላደረገው ድጋፍ በአረጋውያንና በተረጂዎች ስም ምስጋናቸውን ያቀረቡ ሲሆን በቀጣይም ድጋፉን አጠናክሮ እንዲቀጥል ሲሉ ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል፡፡

ግሎባል ባንክ ኢትዮጵያ
ለጋራ ስኬታችን

Related Posts

ግሎባል ባንክ ኢትዮጵያ ከደንበኞች ጋር ያለውን ስትራቴጂካዊ አጋርነት ማጠናከር ዋነኛ መርህ አድርጎ እየሰራ ነው – ዶ/ር ተስፋዬ ቦሩ

ግሎባል ባንክ ኢትዮጵያ ከደንበኞች ጋር ያለውን ስትራቴጂካዊ አጋርነት በማጠናከር ለጋራ ስኬት በጋራ መስራት ዋና ዕሴት አድርጎ እየሰራ መሆኑን...

ባለፉት ዘጠኝ ወራት አመርቂ ዉጤት መመዝገቡ ተገለፀ

ግሎባል ባንክ ኢትዮጵያ ባለፉት 9 ወራት በበርካታ መለኪያዎች አመርቂ ውጤት ማስመዝገቡን የባንኩ የቦርድ አመራር እና የማኔጅመንት አባላት ገለጹ፡፡...

ግሎባል ባንክ ኢትዮጵያ የተሳተፈበት ዓለም አቀፍ የኦቲዝም ቀን በደማቅ ሁኔታ ተከበረ

ነህሚያ የኦቲዝም ማዕከል የ2018 ዓ.ም የኦቲዝም ግንዛቤ ማስጨበጫ መርሃ-ግብርን ሚያዚያ 18 ቀን 2018 ዓ.ም በተለያዩ ዝግጅቶች አከናውኗል።...