
ግሎባል ባንክ ኢትዮጵያ አዲስ ለተመረጡ የቦርድ ሥራ አመራር አባላት የእንኳን ደህና መጣችሁ እና ሥራ የማስጀመሪያ መርሃ ግብር ሰኔ 09 ቀን 2017 ዓ.ም በባንኩ ዋናው መስሪያ ቤት አካሂዷል፡፡
ባንኩ ከዚህ በፊት ይስተዋሉ የነበሩ የአሰራር ክፍተቶችን በማረም እና ጠንካራ ጎኖችን አጠናክሮ በማስቀጠል በማይናወጥ የእድገት ደረጃ ላይ እንደሚገኝ በእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግራቸው የገለጹት የግሎባል ባንክ ኢትዮጵያ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ዶ/ር ተስፋዬ ቦሩ፤ አዲሶቹ የቦርድ አባላት ከባንኩ የማኔጅመንት አባላት ጋረ በመቀናጀት የባንኩን ራዕይ እውን ማድረግ ይጠበቃል ብለዋል፡፡
ባንኩን ላለፉት ዓመታት በብቃት በማገልገል እዚህ ደረጃ ላደረሱት የቀድሞ የቦርድ አመራር አባላት ዶ/ር ተስፋዬ ምስጋናቸውን አቅርበዋል፡፡
አዲሶቹ የቦርድ ሥራ አመራር አባላት አቶ ዮሴፍ ጌታቸውን በቦርድ ሰብሳቢነት እንዲሁም ዶ/ር ዮናስ ሀጎስን ምክትል ሰብሳቢ በማድረግ መርጧል።
ግሎባል ባንክ ኢትዮጵያ ለአዲሶቹ የቦርድ አባላት መልካም የሥራ ጊዜ እንዲሆንላቸው ይመኛል፡፡
ግሎባል ባንክ ኢትዮጵያ
ለጋራ ስኬታችን!