በተሰለፈበት ሁሉ ማሸነፍ የግሎባል ባንክ ኢትዮጵያ መለያ እንዲሆን እየተሰራ ነው – ዶ/ር ተስፋዬ ቦሩ

Share the Post:

ግሎባል ባንክ ኢትዮጵያ በተሰማራበት የሥራ ዘርፍ ሁሉ ቀዳሚ እና አሸናፊ እንዲሆን ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑን የባንኩ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ዶ/ር ተስፋዬ ቦሩ ተናገሩ፡፡

ዶ/ር ተስፋዬ ይኸን ያሉት ግሎባል ባንክ ኢትዮጵያ በአፍሪካ ምርጥ የቁጠባ ባንክ ዘርፍ ተሸላሚ መሆኑንና የባንኩ የእግር ኳስ ቡድን የ2017 ዓ.ም የባንኮች እግር ኳስ ውድድርን በበላይነት ማጠናቀቁን አስመልክቶ ዋንጫውን ለዋና ሥራ አስፈፃሚው ሰኔ 20 ቀን 2017 ዓ.ም በአስረከበበት ወቅት ነው፡፡

ስፖርት ለአእምሮ ጤናና ለአካል ብቃት ግንባታ አይተኬ ሚና እንደሚጫወት የገለጹት ዶ/ር ተስፋዬ ሠራተኞቻችን ንቁ በመሆንና ጤናቸውን በመጠበቅ በቋሚ ስራቸውም አይበገሬ እና አሸናፊ በመሆን የባንኩን ራዕይ እውን ማድረግ ይጠበቅብናል ብለዋል፡፡

ባንኩ ከቅርብ ጊዜ ጀምሮ ኢንዱስትሪው የሚፈልጋቸውን አዳዲስ ቴክኖሎጂዎች በመጠቀም ለደንበኞቻችን ምቹ እና ቀልጣፋ የባንክ አገልግሎት በመስጠት በሀገር አቀፍ እና በዓለም አቀፍ ደረጃ የተለያዩ እውቅናዎችን እያገኘ መሆኑን የገለጹት ዶ/ር ተስፋዬ ወደፊትም በደንበኞች ዘንድ ተመራጭ የባንክ አገልግሎት ከሚሰጡ ባንኮች መካከል ግንባር ቀደም ለመሆን ያላሰለሰ ጥረት እየተደረገ ነው ብለዋል፡፡

የእግር ኳስ ቡድኑ ላስመዘገበው ውጤት ደስተኛ መሆናቸውን የገለጹት ዋና ሥራ አስፈፃሚው ወደፊትም ቡድኑን በሁለንተናዊ መልኩ ለመደገፍ እና ለማበረታታት እንደማይቆጠቡ ተናግረዋል፡፡

የ2017 ዓ.ም የባንኮችን እግር ኳስ ውድድርን ላሸነፈው የግሎባል ባንክ ኢትዮጵያ እግር ኳስ ቡድን አባላት የተለያዩ የማበረታቻ ሽልማቶች ተደርጎለታል፡፡

ግሎባል ባንክ ኢትዮጵያ
ለጋራ ስኬታችን!

Related Posts

ግሎባል ባንክ ኢትዮጵያ ከደንበኞች ጋር ያለውን ስትራቴጂካዊ አጋርነት ማጠናከር ዋነኛ መርህ አድርጎ እየሰራ ነው – ዶ/ር ተስፋዬ ቦሩ

ግሎባል ባንክ ኢትዮጵያ ከደንበኞች ጋር ያለውን ስትራቴጂካዊ አጋርነት በማጠናከር ለጋራ ስኬት በጋራ መስራት ዋና ዕሴት አድርጎ እየሰራ መሆኑን...

ባለፉት ዘጠኝ ወራት አመርቂ ዉጤት መመዝገቡ ተገለፀ

ግሎባል ባንክ ኢትዮጵያ ባለፉት 9 ወራት በበርካታ መለኪያዎች አመርቂ ውጤት ማስመዝገቡን የባንኩ የቦርድ አመራር እና የማኔጅመንት አባላት ገለጹ፡፡...

ግሎባል ባንክ ኢትዮጵያ የተሳተፈበት ዓለም አቀፍ የኦቲዝም ቀን በደማቅ ሁኔታ ተከበረ

ነህሚያ የኦቲዝም ማዕከል የ2018 ዓ.ም የኦቲዝም ግንዛቤ ማስጨበጫ መርሃ-ግብርን ሚያዚያ 18 ቀን 2018 ዓ.ም በተለያዩ ዝግጅቶች አከናውኗል።...