
ግሎባል ባንክ ኢትዮጵያ በተሰማራበት የሥራ ዘርፍ ሁሉ ቀዳሚ እና አሸናፊ እንዲሆን ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑን የባንኩ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ዶ/ር ተስፋዬ ቦሩ ተናገሩ፡፡
ዶ/ር ተስፋዬ ይኸን ያሉት ግሎባል ባንክ ኢትዮጵያ በአፍሪካ ምርጥ የቁጠባ ባንክ ዘርፍ ተሸላሚ መሆኑንና የባንኩ የእግር ኳስ ቡድን የ2017 ዓ.ም የባንኮች እግር ኳስ ውድድርን በበላይነት ማጠናቀቁን አስመልክቶ ዋንጫውን ለዋና ሥራ አስፈፃሚው ሰኔ 20 ቀን 2017 ዓ.ም በአስረከበበት ወቅት ነው፡፡
ስፖርት ለአእምሮ ጤናና ለአካል ብቃት ግንባታ አይተኬ ሚና እንደሚጫወት የገለጹት ዶ/ር ተስፋዬ ሠራተኞቻችን ንቁ በመሆንና ጤናቸውን በመጠበቅ በቋሚ ስራቸውም አይበገሬ እና አሸናፊ በመሆን የባንኩን ራዕይ እውን ማድረግ ይጠበቅብናል ብለዋል፡፡
ባንኩ ከቅርብ ጊዜ ጀምሮ ኢንዱስትሪው የሚፈልጋቸውን አዳዲስ ቴክኖሎጂዎች በመጠቀም ለደንበኞቻችን ምቹ እና ቀልጣፋ የባንክ አገልግሎት በመስጠት በሀገር አቀፍ እና በዓለም አቀፍ ደረጃ የተለያዩ እውቅናዎችን እያገኘ መሆኑን የገለጹት ዶ/ር ተስፋዬ ወደፊትም በደንበኞች ዘንድ ተመራጭ የባንክ አገልግሎት ከሚሰጡ ባንኮች መካከል ግንባር ቀደም ለመሆን ያላሰለሰ ጥረት እየተደረገ ነው ብለዋል፡፡



የእግር ኳስ ቡድኑ ላስመዘገበው ውጤት ደስተኛ መሆናቸውን የገለጹት ዋና ሥራ አስፈፃሚው ወደፊትም ቡድኑን በሁለንተናዊ መልኩ ለመደገፍ እና ለማበረታታት እንደማይቆጠቡ ተናግረዋል፡፡
የ2017 ዓ.ም የባንኮችን እግር ኳስ ውድድርን ላሸነፈው የግሎባል ባንክ ኢትዮጵያ እግር ኳስ ቡድን አባላት የተለያዩ የማበረታቻ ሽልማቶች ተደርጎለታል፡፡
ግሎባል ባንክ ኢትዮጵያ
ለጋራ ስኬታችን!