
የአፍሪካ የባንክ እና ኢንሹራንስ ሽልማት በታንዛኒያ ዋና ከተማ ዳሬሰላም በተለያዩ ዘርፎች የላቀ አፈፃፀም ላስመዘገቡ ባንኮች እና ኢንሹራንሶች የሽማልት ሥነ ስርዓት ሰኔ 06 ቀን 2017 ዓ.ም ተካሂዷል፡፡
በአፍሪካ የባንክ እና ኢንሹራንስ ሽልማት ላይ ግሎባል ባንክ ኢትዮጵያ በአፍሪካ ምርጥ የቁጠባ ባንክ ዘርፍ ተሸላሚ ሆኗል፡፡
በሽልማት ሥነ ሥርዓቱ የዘርፉ ከፍተኛ ባለሙያዎች፣ተመራማሪዎች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ታድመዋል፡፡
ግሎባል ባንክ ኢትዮጵያ ዘመኑ የደረሰበት አዳዲስ ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም ለደንበኞች ምቹ፣ቀላል፣ፈጣን እና አስተማማኝ አገልግሎት እየሰጠ እንደሚገኝ በሽልማት ሥነ ስርዓቱ ወቅት ባደረጉት ንግግር የገለጹት የማርኬቲንግና ኮምዩኒኬሽንስ ዳይሬክተር አቶ ቢኒያም ፍቃዱ ባንኩ ሽልማቱን እንዲያሸንፍ ድርሻቸውን ለተወጡ የባንኩ ሠራተኞች፣ አመራሮች እና ደንበኞች ምስጋናቸውን አቅርበዋል፡፡
ግሎባል ባንክ ኢትዮጵያ በፋይናንስ ዘርፉ ላይ በኢትዮጵያ፣ በአፍሪካ እንዲሁም በመላው ዓለም አወንታዊ ተፅዕኖ በማድረግ ተደራሽ እና ቀልጣፋ የባንክ አገልግሎት ለመስጠት እየሰራ እንደሆነም በሽማልቱ ወቅት ዳይሬክተሩ ገልጸዋል፡፡
ግሎባ ባንክ ኢትዮጵያ በ2016 ዓ.ም በአቢሲንያ የኢንደስትሪ ሽልማት ድርጅት በባንኮች ዘርፍ የወርቅ ደረጃ የኢንደስትሪ ሽልማት አሸናፊ መሆኑ ይታወሳል፡፡
ግሎባል ባንከ ኢትዮጵያ
ለጋራ ስኬታችን!