ግሎባል ባንክ ኢትዮጵያ የአርንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ መርኃግብር አካሄደ

Share the Post:

ግሎባል ባንክ ኢትዮጵያ ሰባተኛውን ዙር የአርንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር ፈረንሳይ ሌጋሲዮን አቢሲኒያ ውሃ ፋብሪካ አካባቢ ሐምሌ 28  ቀን 2017 ዓ.ም አካሄዷል፡፡

በችግኝ ተከላ መርሃ ግብሩ የግሎባል ባንክ ኢትዮጵያ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች፣ የቅርንጫፍ ስራ አስኪያጆች እና ሰራተኞች ተገኝተዋል።

የዘንድሮው የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር “በመትከል ማንሰራራት” በሚል መሪ ቃል በመላው ኢትዮጵያ እየተካሄደ ይገኛል፡፡

ግሎባል ባንክ ኢትዮጵያ ለሰባተኛ ጊዜ አረንጓዴ አሻራ የማኖር መርሃ ግብር ያካሄደ ሲሆን በዛሬው ዕለት ከ5 ሺህ በላይ ችግኞች ተተክለዋል።

ባንኩ ማህበራዊ ኃላፊነቱን በተለያዩ ሁነቶች እየተወጣ የሚገኝ ሲሆን አረንጓዴ አሻራ የማኖር መርሃ ግብር ማህበራዋ ኃላፊነቱን ከሚወጣባቸው ተግባራት መካከል አንዱ ነው።

ዛሬ የተተከሉት ችግኞች በቀጣይ አመታት የተለያዩ ፍራፍሬዎችን የሚሰጡ መሆናቸውን የተናገሩት በችግኝ ተከላ መርሃ ግብሩ የተሳተፉ ሰራተኞች ችግኞቹ እንዲፀድቁ ያልተቆጠበ ክትትል እንደሚያደርጉ አስታውቀዋል።

ግሎባል ባንክ ኢትዮጵያ
ለጋራ ስኬታችን!

Related Posts

ግሎባል ባንክ ኢትዮጵያ ከደንበኞች ጋር ያለውን ስትራቴጂካዊ አጋርነት ማጠናከር ዋነኛ መርህ አድርጎ እየሰራ ነው – ዶ/ር ተስፋዬ ቦሩ

ግሎባል ባንክ ኢትዮጵያ ከደንበኞች ጋር ያለውን ስትራቴጂካዊ አጋርነት በማጠናከር ለጋራ ስኬት በጋራ መስራት ዋና ዕሴት አድርጎ እየሰራ መሆኑን...

ባለፉት ዘጠኝ ወራት አመርቂ ዉጤት መመዝገቡ ተገለፀ

ግሎባል ባንክ ኢትዮጵያ ባለፉት 9 ወራት በበርካታ መለኪያዎች አመርቂ ውጤት ማስመዝገቡን የባንኩ የቦርድ አመራር እና የማኔጅመንት አባላት ገለጹ፡፡...

ግሎባል ባንክ ኢትዮጵያ የተሳተፈበት ዓለም አቀፍ የኦቲዝም ቀን በደማቅ ሁኔታ ተከበረ

ነህሚያ የኦቲዝም ማዕከል የ2018 ዓ.ም የኦቲዝም ግንዛቤ ማስጨበጫ መርሃ-ግብርን ሚያዚያ 18 ቀን 2018 ዓ.ም በተለያዩ ዝግጅቶች አከናውኗል።...