
ግሎባል ባንክ ኢትዮጵያ ከባለአክሲዮኖቹ ጋር ያለውን የስራ ግንኙነት የበለጠ ለማጠናከር የሚያስችለውን የውይይት መድረክ ነሐሴ 18 ቀን 2018 ዓ.ም በዋናው መ/ቤት አካሂዷል፡፡
መድረኩ ባለአክሲዮኖች ስለ ባንኩ ወቅታዊ የፋይናንስ አፈጻጸም፣ የወደፊት ስትራቴጂካዊ አቅጣጫዎችና አጠቃላይ እድገት ግልጽ መረጃ የሚያገኙበት፤ እንዲሁም አስተያየትና ጥያቄዎቻቸውን በቀጥታ ለከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች የሚያቀርቡበት ነው፡፡



ግሎባል ባንክ ኢትዮጵያ ከባለአክሲዮኖቹ ጋር የሚያደርገውን ውይይት ማጠናከሩ፣ በባንኩ እና በባለአክሲዮኖቹ መካከል ያለውን እምነት ለማሳደግ እና ርዕዩን ለማሳካት ትልቅ ሚና እንደሚጫወት በውይይቱ ወቅት ተገልጿል።
የባንካችን ተ/ሥራ አስፈፃሚ አቶ ሳኅለሚካኤል መኮንን እና ከፍተኛ አመራሮች ከባለአክሲዮኖች ለተነሱ ጥያቄዎች ምላሽ እና ማብራሪያ የሰጡ ሲሆን የባንኩን ዘላቂ እድገትና ተወዳዳሪነት ለማረጋገጥ ከባለድርሻ አካላት ጋር የሚደረጉ ተመሳሳይ ውይይቶች በተጠናከረ መልኩ እንደሚቀጥሉ ተመላክቷል።
ግሎባል ባንክ ኢትዮጵያ
ለጋራ ስኬታችን