የግሎባል ባንክ ኢትዮጵያ አመራሮችና ሠራተኞች “ተስፋን እንትከል” በሚል መሪ ቃል ነሐሴ 8 ቀን 2018 ዓ.ም በእንጦጦ ተራራ የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር አካሂደዋል፡፡

ባንካችን ማህበራዊ ኃላፊነቱን የመወጣት ተግባሩን ላለፉት ተከታታይ ዓመታት ሲያከናውን የቆየ ሲሆን፣ የዘንድሮው መርሃ ግብር ለስምንተኛ ጊዜ የተከናወነ ነው። በችግኝ ተከላ መርሃ ግብሩ በርካታ ሀገር በቀል እና ልዩ ልዩ የፍራፍሬ ችግኞች ተተክለዋል።
ባንካችን ከሚሰጠው የፋይናንስ አገልግሎት በተጨማሪ ለማህበረሰብ እና ለአካባቢ ጥበቃ የሚሰጠውን ማህበራዊ ኃላፊነት በቁርጠኝነት እየተወጣ እንደሚገኝ የገለጹት የማርኬቲንግና ኮምዩኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ቢኒያም ፍቃዱ፤ የተተከሉት ሀገር በቀልና የፍራፍሬ ችግኞች ለአየር ንብረት ለውጥና ብክለት መፍትሔ እንዲሆኑ አስፈላጊው ክትትልና እንክብካቤ ይደረግላቸዋል ብለዋል፡፡



ግሎባል ባንክ ኢትዮጵያ ሀገር አቀፉን አረንጓዴ አሻራ የማሳረፍ መርሃ ግብር በመደገፍ በተከታታይ ስምንት ዓመታት በርካታ ችግኞችን በመትከል ለአካባቢ ጥበቃ አዎንታዊ አስተዋጽኦ አድርጓል፡፡
ግሎባል ባንክ ኢትዮጵያ
ለጋራ ስኬታችን