የላቀ አፈፃፀም ላስመዘገቡ ቅርንጫፎች እውቅና ተሰጠ

Share the Post:

ግሎባል ባንክ ኢትዮጵያ በ2024/25 የሒሳብ ዓመት ባንኩ ባስቀመጠው የመለኪያ መስፈርት መሠረት ከፍተኛ ውጤት ላስመዘገቡ ቅርንጫፎች የእውቅናና የሽልማት መርሃ ግብር ሐምሌ 28 ቀን 2017 ዓ.ም ተካሂዷል።

በተቀመጠው የመለኪያ መስፈርት መሠረት ከምስራቅ አዲስ አበባ፣ ከምዕራብ አዲስ አበባ እንዲሁም ከደቡባዊ ዲስትሪክት እስከ ሶስት ለወጡ ቅርንጫፎች በባንኩ ከፍተኛ አመራሮች እውቅና ተሰጥቷል።

አትላስ፣ አዳማፓንአፍሪክ እና ገላን ኮንደሚኒየም ከምስራቅ አዲስ አበባ ዲስትሪክት፤ ኮተቤ፣ፖፑላሬ እና ቀበና ቅርንጫፎች ከምዕራብ አዲስ አበባ ዲስትሪክት እንዲሁም ሚዛን፣ ቡሌሆራ እና ዲላ ቅርንጫፍ ከደቡባዊ ዲስትሪክት ተሸላሚ ሆነዋል።

ክብሩ ፍቃዱ፣ራሄል በቀለ እና ትዕግስት ቦጋለ ደግሞ ከደንበኞች ግንኙነት መምሪያ ላደረጉት ከፍተኛ አስተዋጽኦ እውቅና ሲሰጣቸው፤ ተስፋዬ ገ/መድህን፣ እሱባለው አለምነው እና ኤፍሬም አስፈው አጠቃላይ ካሉ ቅርንጫፎች መካከል ከፍተኛ ውጤት በማስመዝገብ ልዩ ተሸላሚ ሆነዋል።

ግሎባል ባንክ ኢትዮጵያ የተሻለ አፈፃፀም ለሚፈፅሙ ቅርንጫፎች እና ሠራተኞችን ማበረታታት አንዱ ዕሴት መሆኑን በሽልማት መርሃ ግብሩ ወቅት የገለፁት ዋና ስራ አስፈፃሚው ዶ.ር ተስፋዬ ቦሩ በተያዘው የሂሳብ ዓመትም ተሸላሚዎች ይበልጥ እንዲበረቱ እና ሌሎቹ በቀጣይ ተሸላሚ እንዲሆኑ መስራት እንዳለባቸው አሳስበዋል።

ሽልማቱን የተረከቡ የቅርንጫፍ ስራ አስኪያጆች በበኩላቸው ሽልማቱ ይበልጥ እንዲሰሩ እንደሚያነሳሳቸው አውስተው ውጤቱ የመጠው አጠቃላይ ከቅርንጫፍ ሰራተኞች ጋር በመሆኑ በቀጣይም ይኸንኑ ስኬት ለማስቀጠል ቁርጠኞች መሆናቸውን ተናግረዋል።

በዛሬው መርሃ ግብር ከ15 በላይ ቅርንጫፎች እውቅናና ሽልማት ተሰጥቷችዋል።

Related Posts

ባንኩ የተቋቋመበትን ዓላማ እንዲያሳካ ያልተቆጠበ ድጋፍ እናደርጋለን – ከፍተኛ ባለአክሲዮኖች

የግሎባል ባንክ ኢትዮጵያ ከፍተኛ ባለአክሲዮኖች ባንኩ የተጣለበትን ሀገራዊ እና ማህበራዊ ኃላፊነት በተሟላ ሁኔታ ተወጥቶ የተቋቋመበትን ዓላማ እውን...

ግሎባል ባንክ ኢትዮጵያ “ተስፋን እንትከል” በሚል መሪ ቃል የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር አካሄደ

የግሎባል ባንክ ኢትዮጵያ አመራሮችና ሠራተኞች “ተስፋን እንትከል” በሚል መሪ ቃል ነሐሴ 8 ቀን 2018 ዓ.ም በእንጦጦ ተራራ...

ግሎባል ባንክ ኢትዮጵያ የ2025/26 የሥራ አፈጻጸምን ገምግሞ ለ2026/27 ዋና የትኩረት አቅጣጫዎችን አስቀመጠ

ግሎባል ባንክ ኢትዮጵያ የ2025/26 በጀት ዓመት አጠቃላይ የሥራ አፈጻጸም የገመገመበትን መርሃ ግብር ሐምሌ 21 ቀን 2018 ዓ.ም በካፒታል ሆቴል...